Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

News

“የበሽታዎች ቅድመ ትንበያ፣ ቅኝት ምላሽ ላይ ማዕከላት ተቋቁመው ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ ነው። በዚህም የዜጎችን ህይወት መታደግ ተችሏል። ይህ ተግባርም በቴክኖሎጂዎች በመታገዝ ይጠናከራል።”

Abiy Ahmed Ali Website: moh.gov.et Facebook: Ministry of Health,Ethiopia Twitter: x.com/fmohealth YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia Telegram: https://t.me/M0H_EThiopia

በመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ዙሪያ በወጡ አዳዲስ ህጎች ፣መመሪያዎችና የአሠራር ለውጦች ዙሪያ ሐገር አቀፍ የበይነ መረብ ስብሰባ (National Webinars Meeting) 12,000 ተሳታፊዎች በተሳተፉበት እየተካሄደ ነው።

በመድኃኒት አቅርቦት ስርዓት ዙሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለው የበይነ መረብ ስብሰባ የኢፌዴሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ ባስተላለፉት ጥልቅ መልዕከት ተጀምሯል። ሚኒስትሯ በመልዕክታቸው በመድኃኒት አቅርቦት ስርዓት ዙሪያ በወጡ አዳዲስ ህጎች ፣መመሪያዎችና የአሠራር ለውጦች ላይ ሀገራዊ ውይይት ያስፈለገበትን ምክንያት ሲያብራሩ የህዝብን የጤና አገልግሎት ፍላጎት ለማሟላትና በመድሀኒት አቅርቦት ላይ ያለውን ፍላጎት በበቂ…
Read more

ህብረተሰቡን የቁጥጥር ስራው ባለቤት ማድረግ እንደሚገባ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶች ግብአቶች ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታወቀ

ለህብረተሰቡ የሚቀርቡ ምግቦች ደህንነታቸዉና ጥራታቸዉ የተረጋገጠ እንዲሆኑ ለማድረግ የቁጥጥር ስርሃቱን ማጠናከር እንደሚገባ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ የጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶች ግብአቶች ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶች ግብአቶች ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጋር በመተባበር ባዘጋጁት መድረክ መገለፁ ታውቋል ፡፡ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶች ግብአቶች ጥራት ቁጥጥር…
Read more

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2017 በጀት ዓመት የ7 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና March-8 የዓለም የሴቶች ቀን በአለም ለ114ኛ በሃገራችን ደግም ለ49ኛ ጊዜ “ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለዉጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋግጣል!!” በሚል መሪ ቃል በወንዶ ገነት ከተማ የካቲት 29/2017 ዓ.ም ከባለድርሻ አካላት ጋር በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ፤

በመድረኩ ላይ የተገኙት የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር ዳመነ ዳባልቄ ሲሆኑ የሰባት ወር ዕቅድ አፈፃፀምን በተመለከተ ኢንስቲትዩቱ አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን ጠቁመው የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎችን ከመከላከልና ከመቆጣጠር አኳያ ሰፊ የመከላከል ተግባራት የተከወኑ መሆናቸውንና ከተከሰተም በኋላ ምላሽ በመስጠት ረገድ በርካታና ዘርፈ-ብዙ ተግባራት እንደተተገበሩ ገልፀዋል። ከዚህም በተጨማሪ የዓለም የሴቶች ቀንን በተመለከተ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና…
Read more

በሲዳማ ክልል ጤና ተቋማት የሚሰጠው የላቦራቶሪ አገልግሎት ጥራታቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን የሲዳማ ህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ምትክል ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡጋሞ ሀናጋ ገለጸ::

በሲዳማ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የላቦራቶሪ ዳይረክቶሬት የሰባት ወር የስራ አፈጻጸም ገምግሞአል :: በዕለቱ ንግግር ያደረጉት የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይረክተር የሆኑት አቶ ኡጋሞ ሀናጋ በ ክልላችን ያሉ ጤና ተቋማት የሚሰጠው የላቦራቶሪ አገልግሎት ጥራታቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ገልጸው አሁንም በየደረጃ ያሉ ተቋማት የተገኙ ስኬቶችን ለመፈጸም ቁርጠኛ(committed) መሆን እንደሚያስፈልግ አጽንዮት ሰጥተዋል። የሰባት ወር ሪፖርት በላቦራቶሪ ዳይሬክቶሬት ዳይረክተር…
Read more

የተቀናጀ የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ባለፉት 4 ቀናት የእቅዱን 106% ማሳካት መቻሉን የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ጤና እንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳመነ ዳባልቀ አስታወቀ

የዘመቻው የእስከአሁን አፈጻጸም አስመልክቶ በተደረገው ውይይት ላይ የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ጤና እንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳመነ ዳባልቀ እንደገለጹት ባለፉት 4 ቀናት በዘመቻው ከ862835 ለሚሆኑት ህጻናት የፖሊዮ ክትባት ተደራሽ መደረጉን በመግለጽ ይህም የእቅዱን 106% ማሳካት ተችሏል ነው ያሉት። ከክትባት ዘመቻው ጋር የተቀናጁ ትኩረት የሚሹ ተግባራት አፈጻጸም አበረታች ውጤት ተመዝግቦአል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ 2832 ህጻናትን ከክትባት አገልግሎት…
Read more

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የልጅነት ልምሻ (የፖሊዮ )መከላከያ ክትባት ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል ።

የካቲት 14/2017 የሲዳማ ህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ዕድሜያቸው ከ 5 አመት በታች ለሆናቸው ህፃናት ከየካቲት 14-17/2017ዓ.ም የሚሰጠው የመጀመሪያው ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ይፍዊ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በሲዳማ ክልላዊ መንግስት በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሚገኘው በቡልቻ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ተከናውኗል ። የሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ በክትባት ዘመቻው ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በጤናው…
Read more

የመጀመሪያ ዙር የተቀናጀ ልጅነት ልምሻ /ፖሊዮ በሽታን መከላከል ያለመ ክትባት ከየካቲት 14-17/2017 ዓ.ም በዘመቻ እንደሚሰጥ የሲዳማ ክልል መንግስት የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገለፀ

ኢንስቲትዩቱ የዘመቻ ክትባቱን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር የንቅናቄ መድረክ እያደረገ ይገኛል፡ የሲዳማ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ በመልዕክታቸው ፥ የፖሊዮ በሽታን እንደ ሀገር ለማጥፋት ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ ስራዎች ቢሰሩም አሁንም በሽታው አለመጥፋቱን ገልፀዋል ። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም እንደ ሲዳማ ክልል የተከሰተ የፖሊዮ በሽታ ባይኖርም እንደሀገር በሰባት ክልሎችና አዲስ አበባ ከተማ…
Read more