
በዛሬው ዕለት (2/06/2018 ዓ.ም ) የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባዘጋጀው የእውቅና መስጫ ፕሮግራም ላይ ባለፉት ጊዜያት ፥ ማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝንና ሌሎችን ጨምሮ በሀገር እና በክልሎች ደረጃ የተከሰቱ ወረርሽኞችን ለመግታት በሲዳማ ክልል የሚገኙ የጤናው ዘርፍ ተዋናዮች ባሳዩት ቁርጠኝነት በህብረተሰብ ላይ የከፋ ጉዳት ሳያደርሱ በአጭር ጊዜ ወረርሽኞችን መግታት በመቻላቸው ፤ ለክልላችን ጤና ቢሮ ፣ ለህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና ሌሎች የባድርሻ አካላት የዋንጫ እና ሴርቲፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ክልሉ ለዚህ ስኬት እንዲበቃ የበኩላችሁን የተወጣችሁ የየደረጃው ተዋናዮችን ከልብ እናመሠግናለን ።
የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
የካቲት 02/2018 ዓ/ም
ሀዋሳ
ተጨማሪ መረጃዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794
Web site: https://www.sphi.gov.et/













