Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

በማርበርግ ቫይረስ በሽታ መከላከል ላይ ያተኮረ አውደ-ጥናት ከሃይማኖት መሪዎች ጋር ተካሄደ

_____________

መድረኩ የተዘጋጀው በማርበርግ በሽታ ዙሪያ አሁን ያለውን ሁኔታ ለመግለጽ እና የሃማኖት ተቋማት እንዴት በሽታውን መከላከል እንደሚቻል ግንዛቤን ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ የገለጹ ሲሆን፤ ለታማሚዎች በመጸለይ እንዲሁም ታክመው የዳኑ ሰዎች ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ ድጋፍ እንዲያደርጉም መልአክት አስታልፈዋል፡፡ በተጨማሪም የተሳሳተ መረጃን ለማጥራት የሃይማኖት ተቋማት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አክለዋል፡፡

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሃፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር ጉባኤው እንደሃገር የገጠሙንን ተግዳሮቶች ለመፍታት እንደሁልጊዜውም ከጤና ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡ ከባህል እና ከልምድ ጋር በተያያዘ የሚስፋፉ በሽታዎችን ለመከላከል የሃይማኖት ተቋማት ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር አይተኬ ሚና አላቸው ብለዋል፡፡

የማርበርግ በሽታን በመቆጣጠር ሂደት የሃይማኖት መሪዎች ላሳዩት ተሳትፎ ምስጋና ያቀረቡት የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ዶ/ር መልካሙ አብቴ፤ የሃይማኖት መሪዎች ራሳቸውን ከበሽታው በመጠበቅ ሌሎችን ማስተማር ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡

#MarburgVirus

Website: moh.gov.et

Facebook: Ministry of Health,Ethiopia

Twitter: x.com/fmohealth

YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia

Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia

Telegram: t.me/M0H_EThiopia

Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *