Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

የአደጋ ጊዜ ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድኖች የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ወደ ተገኘበት አካባቢዎች ተልከው ቫይረሱን የመከላከልና የመቆጣጠር ስራ እየተሰራ ይገኛል

____________

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በወቅታዊ የጤና ጉዳይ ላይ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጅንካ ከተማ የማርበርግ ቫይረስ በሽታ መከሰቱ በላቦራቶሪ መረጋገጡ መገለጹን ያስታወሱት ሚኒስትሯ እስካሁንም ድረስ 17 የተጠረጠሩ ሰዎች ምርመራ ተደርጎላቸዋል፣ ከዚህም 3ቱ ህይወታቸው በቫይረሱ ያለፈ መሆኑን በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ኢንስቲትዩት ሪፈረንስ ላቦራቶሪ መረጋገጡ፣ በተጨማሪም በምርመራ የተረጋገጠ ባይሆንም 3 ምልክቶች የታየባቸው ሰዎችም ህይወት ማለፉን ገልጸዋል። ሌሎች ንኪኪ የነበራቸዉ 129 ሰዎች ራሳቸዉን ለይተዉ ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል። በቫይረሱ ህይወታቸዉን ላጡ ወገኖች የተሰማቸዉን ሀዘን በመግለጽ ለቤተሰቦቻቸዉና ወዳጅ ዘመዶቻቸዉ መጽናናትን ተመኘተዋል

መንግስት በራስ አቅም ከፍተኛ የላቦራቶሪ አቅም በመገንባት የዘረ-መል ምርመራ ጭምር በሀገር ዉስጥ ማድረጉን የተናገሩት ዶ/ር መቅደስ በዛሬዉ ዕለት ከፍተኛ የመመርመር አቅም ያለዉ ተንቀሳቃሽ ላቦራቶሪም ወደ ጅንካ መላኩን ተናግረዋል።

ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድኖች ቫይረሱ ወደ ተገኘባቸው አካባቢዎች ተልከዋል፣ የተቀናጀ የአስቸኳይ ጊዜ ምላሽ መስጠትም ተጀምሯል። የአደጋ ጊዜ ፈጣን ምላሽ ሰጪ ማእከላትና የህክምና ተቋማትን ማቋቋምና ማጠናከር ስራ ተጠናክሮ እየተሰራ ይገኛል። የህክምና አቅርቦቶች እና የኢንፌክሽን መከላከያ ቁሳቁሶች ስርጭትም እየተከናወነ ነዉ።

የህብረተሰብ ግንዛቤ ማስጨበጫና የቅኝትና ቁጥጥር ስራዎች እየተካሄዱ ሲሆን በሀገር ውስጥና በድንበር አከባቢ መግቢያ እና መውጫ ቦታዎች ላይ የጤና ምርመራዎች እየተጠናከሩ መሆኑን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ ገልጸዋል።

ምልክቶቹ ከፍተኛ ትኩሳት፣ ራስ ምታት፣ የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ እና ደም መፍሰስ ይገኙበታል። የበሽታው ምልክት የታየበት ማንኛውም ሰው ወደ ጤና ተቋም መሄድ ወይም በነፃ የስልክ መስመሮች 8335 ወይም 952 መደወል አለበት።

ወረርሽኙን ለመቆጣጠር እና ማህበረሰባችንን ለመጠበቅ ጠንክረን እየሰራን ነው ሲሉ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተናገሩ ሲሆን ህብረተሰባችን የመከላከያ እርምጃዎችን እንዲከተል፣ ምልክቶቹ ከታዩ ወዲያውኑ ወደ ጤና ተቋም እንዲሄድ እና ከጤና ባለሙያዎች ጋር እንዲተባበር ጥሪ አቅርበዋል።

ሙሉ መግለጫውን ሊንኩን ተጭነው ማግኘት ይችላሉ፡ https://www.moh.gov.et/…/Marburg_Virus_Disease_Press…

Website: moh.gov.et

Facebook: Ministry of Health,Ethiopia

Twitter: x.com/fmohealth

YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia

Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia

Telegram: t.me/M0H_EThiopia

Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *