Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

የሲዳማ ብ/ክ/መ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የላቦራቶሪ መሳሪያዎችን ለተቋማት ርክክብ አደረገ።

በርክክቡ ላይ የተገኙት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ እንደገለጹት በጤና ሚኒስትር እና በኢ/ህ/ጤ ኢንስቲትዩት ድጋፍ የተገኙት በድምሩ ከ3,000,000 ብር በላይ የሚገመት በአይነት የተለያዩ መሳሪያዎች ተበርክቷል ብሏል።

አክለውም የናሙና ቅብብሎሽን ለማጠናከር ትሪፕል ፓኬጆችን፤የውጫዊ ጥራት ቁጥጥር መረጃ ለማጠናከር ኮምፒውተር እና ለተበላሸባቸው ማይክሮስኮፒም ጭምር መሰጠቱን ገልፀው ; ለታለመለት አላማ ብቻ እንድውል መልእክት አስተላልፈዋል።

በተጨማርም ኢንሰቲትዩቱ የዛሬውን ጨምሮ በ2017 በጀት ዓመት የ27,000,000 ብር የህክምና ቁሳቁሰና መድሃኒት ለተቋማት ድጋፍ ማድረጉን ኃላፊው አክለው ገልጿል ።

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

ሀምሌ 28/2017 ዓ/ም

ሀዋሳ

ተጨማሪ መረጃዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794

Web site: https://www.sphi.gov.et

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *