Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የጤና ትብብርን ለማጠናከር የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ

__________

በኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር እና በሩሲያ የሸማቾች መብት ጥበቃ እና የሰብአዊ ደህንነት ክትትል አገልግሎት የመግባቢያ ስምምነቱ ተፈርሟል። ፊርማው የተካሄደው ለመጀመሪያ ጊዜ የሩሲያ-አፍሪካ ለድንገተኛ የጤና አደጋዎች ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድኖች ልምምድ እና አውደ-ጥናት መርሃ-ግብር ጎንዮሽ ሲሆን፤ በጤና ድንገተኛ አደጋዎች ላይ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር ያለመ ስምምነት ነው፡፡
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ኢትዮጵያን ወክለው፣ የሩስያ የሸማቾች መብት ጥበቃ እና የሰብአዊ ደህንነት ክትትል አገልግሎት ኃላፊ አና ፖፖቫ ሀገራቸውን ወክለው ፈርመዋል። ይህ የመግባቢያ ሰነድ ከጤና እና ንፅህና ጋር በተያያዙ ድንገተኛ ሁኔታዎች በተለይም በወረርሽኝ ወይም የጤና አደጋዎች በሚከሰቱበት ጊዜ የሚሰጥን ፈጣን ምላሽን በማሻሻል ላይ ያተኮረ ነው።
በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ ዶ/ር መቅደስ ዳባ በጤና ላይ አለም አቀፍ ትብብር ያለውን ጠቀሜታ አጽንኦት ሰጥተዋል። በትብብር መስራት ሀገራት እውቀትና ሃብት እንዲለዋወጡ የሚያስችል መሆኑን ገልጸው፤ ይህም የጤና ድንገተኛ አደጋዎችን በብቃት ለመቆጣጠር ወሳኝ ነው ብለዋል።
አና ፖፖቫ የዚህን ስምምነት አስፈላጊነት በማጉላት ሁለቱም ሀገራት ለድንገተኛ የጤና አደጋዎ በተሻለ ሁኔታ እንዲዘጋጁ እና የዜጎቻቸውን ደህንነት ለመጠበቅ እንደሚረዳ አስረድተዋል። ትብብሩ የእያንዳንዱን ሀገር የጤና ስጋቶች ምላሽ የመስጠት አቅምን ለማሳደግ መረጃን መለዋወጥ፣ ስልጠና እና ምርጥ ተሞክሮዎችን መጋራትን ያካትታል።
ይህ ስምምነት በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል በጤናው ዘርፍ ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ወሳኝ እርምጃ ነው። ሁለቱም ሀገራት የጤና ድንገተኛ ሁኔታዎች ሲገጥሟቸው በፍጥነት እና በብቃት እንዲሰሩ እና በመጨረሻም የህዝብ ጤናን ለህዝቦቻቸው እንዲያሻሽሉ ለማድረግ ያለመ ነው።
የመግባቢያ ሰነዱ በተፈረመበት መድረክ ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ተንቀሳቃሽ ላብራቶሪ ከነ ሙሉ መሳሪያዎቹ የሩሲያ መንግስት ድጋፍ አድርጓል።
Ethiopia, Russia sign MoU to strengthen health cooperation
____________
The Ethiopian Ministry of Health and the Russian Consumer Rights Protection and Human Wellbeing Monitoring Service have signed a Memorandum of Understanding. The signing took place on the sidelines of the first-ever Russia-Africa Emergency Response Teams Exercise and Seminar Program, an agreement aimed at strengthening cooperation between the two countries on health emergencies.
Minister of Health Dr. Mekdes Daba signed on behalf of Ethiopia, while Anna Popova, Head of the Russian Consumer Rights Protection and Human Wellbeing Monitoring Service, signed the MoU on behalf of her country. The MoU focuses on improving the rapid response to health and hygiene emergencies, especially during epidemics or health disasters.
During the signing ceremony, Dr. Mekdes Daba stressed the importance of international cooperation in health. She said that working together allows countries to share knowledge and resources, which is crucial for effectively managing health emergencies.
Anna Popova emphasized the importance of this agreement, explaining that it will help both countries better prepare for health emergencies and protect the safety of their citizens. The cooperation includes exchanging information, training, and sharing best practices to enhance each country’s capacity to respond to health threats.
This agreement is a significant step in advancing the relationship between Ethiopia and Russia in the health sector. It aims to enable both countries to respond quickly and effectively when faced with health emergencies and ultimately improve public health for their populations.
At the signing ceremony, the Russian government provided a mobile laboratory worth over 110 million birr, complete with all the necessary equipment
Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia
Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia
Telegram: https://t.me/M0H_EThiopia

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *