
በክልላችን የሚገኙ አራት ሆስፒታሎች በዛሬው ዕለት በጤና ሚኒስቴር ፤ በ4ኛው ዙር የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት ( EHAQ 4th Cycle) ውድድር ባስመዘገቡት የተሻለ አፈጻጸም የገንዘብ እና የዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል።
በዚሁ መሠረት:-
1.ይ/ዓለም ሕክምና ኮሌጅ አ/ ሆስፒታል 2ኛ ደረጃ በመውጣት የ3,000,000 እና የብር ዋንጫ
2.ለኩ አ/ሆስፒታል ፣ አዳሬ አ/ሆስፒታል እና ሞቲቴ ፉራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል 3ኛ ደረጃ በመውጣት እያንዳንዳቸው 2,000,000 ብር እና የነሐስ ዋንጫ ተሸልመዋል።
በሀገር ደረጃ ከተሸለሙት ከ30 ሆስፒታሎች ከላይ የጠቀስናቸው ሆስፒታሎቻችን ባገኙት ዕውቅና የክልሉ ጤና ቢሮ የተሰማውን ልባዊ ደስታ ይገልጻል።
የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
27/06/ 2018 M.D
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
![]()
![]()
![]()
ይመልከቱ
Website: https://www.shb.gov.et
Facebook:
Telegram : https://t.me/SidamaRHB
Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau
WhatsApp:
YouTube:
Tik Tok:













