Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ወደ ሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ ከተማ ሀዋሳ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው !

የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ታህሳስ 03/2018 ዓ.ም

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሀገር አቀፍ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻን በይፋ ለማስጀመር ወደ ሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሀዋሳ ከተማ ሲደርሱ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል ።

በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻን ፣ የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ፣የኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ሀዋሳ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ዘመን ለገሰ እንዲሁም የቢሮው የማኔጅመንት አካላት ሀዋሳ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ክብርት ሚኒስትሯን፣ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ሀይሉን እንዲሁም አብረዋቸው የተገኙ እንግዶችን በሙሉ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት በክልሉ ጥሩ የቆይታ ጊዜ እንዲኖራቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት

ታህሳስ 03/2017 ዓ.ም

ሐዋሳ

ተጨማሪ መረጃዎችን የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794

Web site: https://www.sphi.gov.et/

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *