Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

Month: December 2025

የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ወደ ሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ ከተማ ሀዋሳ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው !

የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ታህሳስ 03/2018 ዓ.ም የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሀገር አቀፍ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻን በይፋ ለማስጀመር ወደ ሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሀዋሳ ከተማ ሲደርሱ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል ። በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻን ፣ የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ፣የኢትዮጵያ…
Read more

ከ25 ሚሊዮን በላይ ህፃናት የፖሊዮ ክትባት ሊከተቡ ነው

—————— በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከ25 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ህፃናት ተደራሽ ለማድረግ አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለጸ፤ የመጀመሪያው ዙር የክትባት ዘመቻም ከታህሳስ 3 እስከ 6/2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ይጠበቃል። ይህ የተገለፀው የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለብሔራዊ ሚዲያ ባለሙያዎች እና ለሚኒስቴሩ ተጠሪ ተቋማት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች ህዳር 30| 2018 ዓ.ም…
Read more

የማርበርግ ቫይረስ በሽታን የመከላከልና የመቆጣጠር ስራ የሁሉንም ዜጋ ርብርብ ይሻል አቶ በድሉ ባዴጎ።

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ህዳር 30/2018 ዓ.ም የማርበርግ ቫይረስ በሽታን የመከላከልና የመቆጣጠር ስራ የሁሉንም ዜጋ ርብርብ እንደሚሻ የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በክልሉ ለሚገኙ የሀይማኖት ተቋማት በሁለት ዙር ሲሰጥ በነበረው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ ተገልጿል። የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ በድሉ ባዴጎ በመልዕክታቸው የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በርካታ…
Read more

አንድም ህጻን በፖሊዮ በሽታ እንዳይያዝ ሁሉም የራሱን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ ተገለጸ

———————– የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከጤና ሚኒስቴር እና ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ሀገር አቀፍ የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የንቅናቄ መድረክ ህዳር 29/2018 ዓ.ም በአዳማ ከተማ አካሄደ፡፡ የንቅናቄ መድረኩ ዋና ዓላማ አሁናዊ የፖሊዮ ስርጭት እንደ ሀገር ምን እንደሚመስል ግንዛቤ ለመፍጠር ፣ ከታህሳስ 3 እስከ 6/2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ሁገር አቀፍ የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የሚከናወኑ ተግባራት ላይ…
Read more

የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ የሀይማኖት ተቋማት ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባ ተገለፀ፡፡

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ህዳር 30/2018 ዓ/ም የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለሀይማኖት ተቋማት በማርበርግ ቫይረስ በሽታ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቷል። የኢንስቲትዩቱ የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ በድሉ ባዴጎ ባስተላለፋት መልዕክት የማርበርግ ቫይረስ በሀገራችን መከሰቱ ከታወቀበት ጊዜ ጀምሮ ወረርሽኙን አስቀድሞ ለመከላከልና ለመቆጣጠር በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልፀዋል። አቶ በድሉ አክለውም ስራውን…
Read more

እንኳን ለ20ኛው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!

በዓሉን ስናከብር ራሳችንን ከማርበርግ ቫይረስ በሽታ እንጠብቅ #MarburgVirus የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲዩት ህዳር 29/2017 ዓ.ም ሐዋሳ ተጨማሪ መረጃዎችን የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794 Web site: https://www.sphi.gov.et/

በሲዳማ ክልል የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በመከላከል እና በመቆጣጠር መደበኛ የጤና ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባቸው ተገለፀ።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሕዳር 28/2018 ዓ.ም የማርበርግ ቫይረስ በሽታ በመከላከል እና በመቆጣጠር መደበኛ የጤና ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው ፤ቢሮው ከጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችና ከወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊዎች ጋር ባካሄደው የአፈጻጸም ግምገማ ላይ መገለፁ ታውቋል ፡፡ መድረኩን በመምራት መልዕት ያስተላለፉት የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትልና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ሀላፊ አቶ በላይነህ በቀለ በንግግራቸው ፥ እንደ ክልል…
Read more

የማርበርግ ቫይረስን ለመግታት በሚደረገው ጥረት የሚረዳ የቻይናው ኮመን ድርጅት የአየር መተንፈሻ ማሽኖች ድጋፍ አደረገ

___________ የማርበርግ ቫይረስ ህክምና ለማህበረሰቡ በተሻለ መልኩ ለመስጠት እገዛ የሚያደርጉ ሜካኒካል የአየር መተንፈሻ ( Mechanical Ventilator ) ቻይና ሀገር የሚገኝ ኮመን የተባለ ድርጅት ድጋፍ ያደረገ ሲሆን፤ የድርጀቱ የምስራቅ እና የሰሜን አፍሪካ የሽያጭ እና ግብይት ዳይሬክተር ፍራንክ ያንግ ለጤና ሚኒስትር ዴኤታዋ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ አስረክበዋል። የማርበርግ ቫይረስ ለመቆጣጠር ጥረት እየተደረገ ባለበት ወቅት የህክምና መገልገያ ማሽኖቹ ድጋፍ…
Read more

የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር በማርበርግ ቫይረስ በሽታ ዙሪያ ለሃይማኖት ተቋማት ኃላፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሕዳር 26/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ለሃይማኖት ተቋማት መሪዎች በማርበርግ በሽታ ምንነት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥተዋል ፤ በሚጠበቅባቸውም ሚና ዙሪያ ሰፊ ውይይት አካሂደዋል። በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ የተገኙት የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ በመልዕክታቸው ፦የማርበርግ ቫይረስ…
Read more

የማርበርግ ቫይረስ ምላሽን ለማሳደግ የሚረዳ የሙከራ ክትባት ለተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች ሊሰጥ ነው

___________ የማርበርግ ቫይረስ ምላሽ ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት የሚደግፍ 2,500 የማርበርግ ቫይረስ የሙከራ ክትባት ከአሜሪካ መንግስት በድጋፍ የተገኘ ሲሆን፤ ክትባቱን ለኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት የአሜሪካ በኢትዮጵያ አምባሳደር አርቪን ማሲንጋ አስረክበዋል። ክትባቱ በአርማወር ሃንሰን የምርምር ተቋም በሚመራ ፈጣን የደረጃ 2 ክሊኒካዊ ሙከራ ተደርጎለት ጥቅም ላይ እንደሚውል የገለጹት ክትባቱን የተረከቡት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሲሆኑ፣ የምርመራ ተቋሙ…
Read more