Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት መንግሥታዊ ካልሆነ ድርጅት ICAP ጋር በመሆን ለሲ/ብ/ክ/መ/ ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ስር ላሉ ጤና ተቋማት የmicroscope ድጋፍ አደረጉ ::

=========================

የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ለሲዳማ ክልል ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ያደረገዉ የማይክሮሰኮፕ ድጋፍ ርክክብ ተከናወነ።

በርክክቡ ስነ-ስርዓት ላይ የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ዋና አሰተዳደር አቶ ግዛቸዉ ኖኦራ ፥ ለኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና በማቅረብ ይህ ድጋፍ በሲ/ብ/ክ/መንግስት ያለውን ጠንካራ አጋርነት ያሳያል ብለዋል።

ዋና አስተዳዳሪው አክለውም በቀጣይም እንዲህ ዓይነት ድጋፍ ተጠናክሮ እንድቀጥል ያላቸዉን እምነት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ በበኩላቸው EPHI በጤናው ዘርፍ ያሉ ማነቆዎችን ለመፍታት ለሀገርቱ ክልሎች ለተለያዩ ጤና ተቋማት ድጋፍ እየተሰጠ የቆየ ተግባር መሆኑን አስታውሰው ፤ በዚህ ማዕቀፍ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩትና የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ሁልጊዜም ተቆራኝተው ሲሰሩ መቆየታቸዉን በመግለፅ ዛሬ ለዞኑ የተበረከተው የምርመራ microscope ውጤታማ በሆነ መንገድ ጥቅም ላይ እንድዉሉ መልዕክት በማስተላለፍ ፤ ከሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ጋር ቀጣይነት ያለው ድጋፍ እና ትብብር ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

ሀምሌ 02/2017 ዓ/ም

ሀዋሳ

ተጨማሪ መረጃዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794

Web site: https://www.sphi.gov.et/

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *