Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

የሲዳማ ሕብረተስብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2017 በጀት አመት የኤች አይ ቪ ቅኝት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በሀዋሳ ከተማ እየገመገመ ይገኛል።

የመክፈቻ ንግግር በማድረግ የውይይት መድረክ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት PHEM ዳይሪክቶሬት ዳይሬክተር አቶ በድሉ ባዴጎ የኤች አይ ቪ ሥርጭትን ለመግታት እየተሰሩ ያሉ የቅኝት ሥራዎች አበረታች መሆኑን ጠቅሰው በተለይ ተጋላጭ የሆኑ ማህበረሰብ አባላት ላይ የበለጠ ትኩረት ተሰጥቶ በመሠራቱ አበረታች ዉጤት መመዝገቡን አሳስበዋል።

በመቀጠልም የዓመቱ የኤች አይ ቪ ሰርቪላንስ ሪፖርት ዶ/ር አፌንሻ አመሎ ካቀረቡ በኋላ ጠንካራ ውይይት በማድረግ ጥንካሬና ክፍተት በመለየት ቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ ለመደገፍ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት

ነሐሴ 12/2017ዓ.ም

ሀዋሳ፣ ሲዳማ

ተጨማሪ መረጃዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794

Web site: https://www.sphi.gov.et

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *