Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

በሲዳማ ክልል ባለፉት ዓመታት የጤና ተቋማትን ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ስራዎች ተከናውኗል፦

የሲዳማ ክልል ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ፣ሚያዝያ 20/2017 ዓ.ም
በክልሉ የጤና ተቋማትን ተደራሽነት ለማረጋገጥ በተሰራዉ ስራ ከክልል ምስረታ በፊት 16 ሆስፒታሎች ከነበሩበት በአሁኑ ጊዜ ወደ 21 ከፍ ማድረግ ተችሏል።
በአሁኑ ሰዓት በክልሉ 1 ኮንፕሬንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን ጨምሮ 7 አጠቃላይ ሆስፒታሎች እና 14 የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች በድምሩ 22 ሆስፒታሎች አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
ከዚህ በተጨማሪ የክልሉ መንግሥት ከፍተኛ በጀት በመመደብ 1 አዲስ ሆስፒታል ግንባታ እና 3 ነባር ሆስፒታሎች የማስፋፊያ ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
የክልሉ መንግሥት በጤናዉ ዘርፍ በሠጠው ትኩረት ፣ ከክልል ምስረታ በፊት 134 ጤና አጠባበቅ ጣቢያዎች የነበረው በአሁኑ ጊዜ 142 ልደርስ ችሏል፡፡
ከዚህም ጋር ተያይዞ 6 አዳዲስ እና በሌሎች ነባር ጤና አጠባበቅ ጣቢያዎች የማስፋፊያ ግንባታዎች በክልሉ በሁሉም አከባቢዎች በልዩ ትኩረት እየተገነቡ ያሉ ስሆን ፣ ይህም የክልሉን የጤና ተቋማት ተደራሽነትን ለማሳደግ የማይተካ ሚና ይኖረዋል።
በክልሉ በአሁኑ ጊዜ የጤና ተቋማት አገልግሎት ሽፋን ከ70% በታች የነበረዉን ወደ 78% በላይ ከፍ ማድረግ ተችሏል።
በክልሉ “ለበለጠ ዉጤት እንስራ! ” በሚል ኢንሼቲቭ በተካሔደው ንቅናቄ በድምሩ 247 አዲስ ጤና ኬላዎች ጥገና እና አዲስ ግንባታ በህብረተሰብ ተሳትፎ ተከናዉኗል፡፡
ለበለጠ መረጃ
➚ድረ ገጽ፦ https://sidamanrsps.gov.et
➚ፌስቡክ፡- Sidama National Regional State Communication Affairs Bureau
➚ዩትዩብ፦https://youtube.com/@snrscom.bureau?si=r5EAWg8x4kXmLqQN
➚WhatsApp https://whatsapp.com/channel/0029VadMPA2DDmFbMwfTjG3l
➚ቴሌግራም፦ https://t.me/SidamaCommunicationbureau፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *